Wednesday, March 19, 2014

በእስር ላይ የሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ጉዳይ በድጋሜ ተቀጠረ

መጋቢት ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አለማቀፍ የሴቶችን ቀን ምክንያት በማድረግ በተዘጋጀ ሩጫ ላይ ተቃውሞ አሰምታችሁዋል በሚል ከአስር በላይ ቀናትን በእስር ያሳለፉት የሰማያዊ ፓርቲ 7 ሴት እና 3 ወንድ አመራሮች መጋቢት 5 ቀን 2006 ዓም ጉዳያቸው ለመጨረሻ ጊዜ እንደሚታይና ለዛሬ መጋቢት 9 ውሳኔ እንደሚሰጣቸው በዳኛው ተገልጾ የነበረ ቢሆንም፣ ፖሊስ ጉዳዩ በመደበኛ ፍርድ ቤት እንዲታይ በመጠየቁ ፍርድ ቤቱ ለነገ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ፖሊስ ከዚህ ቀደም ምርመራውን በ5 ቀናት አጠናቆ ክስ እንዲመሰርት ቢታዘዘም ፣ ዛሬ የሚያዙ ተጨማሪ 20 ሰዎች አሉ በሚል ተጨማሪ የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል።ጠበቃ አለሙ ጎቤቦ ግን የፖሊስን ጥያቄ አጥብቀው ተቃውመዋል።
ወጣቶቼ የፓርቲው የአመራር አባላት በእስር ቤት ውስጥ መብታቸው እየተጣሰ መሆኑን ገልጸዋል።

No comments:

Post a Comment