Monday, December 29, 2014

የኢሳት 4ኛ አመት በበርገን ከተማ ኖርዌይ ተከበረ

 የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን (ኢሳት) የተመሰረተበትን አራተኛ አመት በዓል ምክንያት በማድረግ ተጋባዥ የኢሳት ጋዜጠኞች ከእንግሊዝ አበበ ቶላ እና ፍስሐ ተገኝ ከአመስተርዳም ገሊላ መኮንን እንዲሁም በኖርዌይ የሚኖሩ የኢሳት ቤተሰቦች በተገኙበት “ኢሳት ይቀጥላል”  በሚል መሪ ቃል ቅዳሜ ዲሴምበር 13 . 2014 በደመቀ ሁኔታ በኖርዌይ በርገን ከተማ ተከብሮ ውሏል ፡፡


             
በእለቱ የነበረውን ፕሮግራም የኢሳት በርገን ቅርጫፍ ድጋፍ ሰጭ ሊቀመንበር አቶ ሰለሞን አሸናፊ እና ጋዜጠኛ ገሊላ መኮንን በአማረ መልኩ መርተውታል ፡፡ ዝግጅቱን በንግግር የከፈተው የኢሳት በርገን ፀሐፊ የሆነው ወጣት ሺበሺ ጌታቸው ሲሆን ንግግሩም ያተኮረው  “ኢሳት ይቀጥላል”  ስንል ምን ማለታችን ነው በማለት ሰፋ ያለ ማብራሪያ አቅርቧል በተጨማሪም በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም አይነት ነፃ ሚዲያ ባለመኖሩ ይህንን ክፍተት ለመሸፈን ኢሳት የኢትዮጵያን ህዝብ በመረጃ ሙሉ ከማድረግ አንፃር እየሰራ ያለውን ስራ አድንቀዋል ፡፡  ኢሳት የህዝባችን አንደበት፣አይን እና ጆሮ ስለሆነ ኢሳትን ለመርዳትና ቋሚ አባል በመሆን የዜግነት ግዴታችንን በመወጣት  በመረጃ እጦት ውስጥ ላለው ወገናችን አለኝታ እንድንሆንና የኢሳትን ቀጣይነት ለማረጋገጥ  የኛ ድጋፍ ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለው አስገንዝበዋል ፡፡
               
      በቀጣይነትም  የኢሳትን ስራ የሚዘክር የኢሳት መዝሙር በአቶ ማርቆስ አብይ ተደርሶ በቶማስ  አለባቸው ዜማው ተሰርቶ በአቶ ኢሳያስ አዘጋጅነት ተዘጋጅቶ ቀርቧል ፡  የመዝሙሩ መጠሪያ “ኢሳት ይቀጥላል በፍጹም አይቆምም ” የሚል ሲሆን በህብረት ዘማሪያን ለታዳሚው ቀርቦ ከፍተኛ አድናቆትን አትርፏል ፡፡ መዝሙሩም በሲዲ ተቀርፆ ለኢሳት ኖርዌይ በስጦታ ተበርክቷል ፡፡
       በመቀጠል ተጋባዥ የኢሳት እንግዶች ጋዜጠኛ አበበ ቶላ እና ጋዜጠኛ ፍሰሐ ተገኝ በወቅታዊ የሃገራችን ጉዳዮች እና በኢሳት ዙሪያ  አዝናኝና አስተማሪ የሆኑ ገጠመኞቻቸውን ለታዳሚው እያዋዙ አቅርበዋል ፡ በተጨማሪ ጋዜጠኛ ገሊላ መኮንን  በነፃነት ታጋዩ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ዙሪያ የሚያተኩር ስሜትን የሚነካ ግጥም ያቀረበች ሲሆን ታዳሚውም  በአፀፋው ለሶስቱ ጋዜጠኞች ያለውን ፍቅርና አክብሮት በጭብጨባ ገልፀውላቸዋል ፡፡

 ሌላው በእለቱ ለየት ያለ ዝግጅት የቀረበው የኢሳት የሶስቱም ስቱዲዮ ጋዜጠኞች የሚያቀርቧቸውን ዝግጅቶች የሚዘክር የፎቶ  ኤግዚብሽን  ለእይታ የቀረበ ሲሆን በእያንዳንዱ ስቱዲዮ የሚቀርቡትን ዝግጅቶች ማለትም አቶ ሚካኤል አቦዬ  የአመስተርዳም ስቱዲዮን ፣ አቶ አሰግድ ታመነ  የዋሽንግተን ስቱዲዮን እና አቶ ዳዊት ዮሐንስ የለንደን ስቱዲዮን ዝግጅቶች ለጎብኚዎቹ በስፋት አብራርተዋል ፡፡
   
ሌላው በዝግጅቱ ላይ የቀረበው “የሳኦል ፍሬዎች” የሚል በአቶ አይንሸት ገበያው ተደርሶ በገሊላ መኮንን አዘጋጅነት በቅርቡ በዋሽንግተን ዲሲ ለእይታ የሚቀርበው ፊልም የተመረቀው በዚሁ እለት ነበር ፡፡ ይህ ፊልም  በሃገራችን ወቅታዊ ጉዳይ ላይ የሚያተኩር ሲሆን በአጭሩ ለተመልካች ቀርቧል ፡፡ በተጨማሪም በኢሳት ላይ የሚያተኩር እና መሳጭ ግጥም በወጣት ዳዊት እዮብ ቀርቦ ከተመልካች አድናቆትን አትርፏል ፡፡

 በመጨረሻም የቀረበው የአትሌት ሙሉጌታ ዘውዴ በኖርዌይ “በርገን ሲቲ” በሚል የሚዘጋጀውን የግማሽ ማራቶን  ውድድር  የኢሳትን ቲሸርት በመልበስ   ሮጦ ያሸነፈበትን ዋንጫ ለጫረታ አቅረቦ በተለይም በኦስሎ እና በበርገን ከተሞች የመጡ የኢሳት ቤተሰቦች ከፍተኛ የሆነ ፉክክር ያደረጉበት ሲሆን በመጨረሻም ከኦስሎ የመጣው አቶ ፋንታሁን ተሰማ  በከፍተኛ ገንዘብ ጨረታውን አሽንፎ ዋንጫውን የግሉ አድርጓል በተጨማሪም  አትሌት ሙሉጌታ ዘውዴ  “በበርገን ፋና ግማሽ ማራቶን” ያሸነፈበትን ዋንጫ ለኢሳት በስጦታ መልክ አበርክቷል ፡፡ በዕለቱ ከጫረታ፣ ከትኬት እና ከመስተንግዶ ከ 100000.00 / ከመቶ ሺህ ክሮነር/ በላይ መስብሰቡን በበርገን የኢሳት የገቢ ማሰባሰብ ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ባጫ ደበሌ ለተሰብሳቢው ይፋ አድርገዋል ፡፡
       
 የዝግጅቱም ፍፃሜ ለተጋባዥ ጋዜጠኞች እና ለኢሳት ቤተሰቦች  እንኳን ለ4ኛ አመት አደረሳችሁ በሚል የተዘጋጀውን ኬክ የመቁረስ ስነ ስርዓት ተካሂዶ  “ኢሳት ይቀጥላል በፍጹም አይቆምም “ በሚለው መዝሙር ታጅቦ በተሳካ እና አስደሳች በሆነ ሁኔታ ተጠናቋል  ፡፡
                                                   
                                                                                             ኢሳት ይቀጥላል
                                                                                               ዳዊት እያዩ
                                                                               በኖርዌይ የኢሳት በርገን ቅርጫፍ  ድጋፍ ሰጪ  




Friday, December 12, 2014

የኢትዮጵያ መንግሥት ገመና (ተመስገን ደሳለኝ)

ተመስገን ደሳለኝ  (ከዝዋይ እስር ቤት)
መሐሙድ የሱፍ የተወለደው በ1980ዓ.ም ከሶማሌ ክልል ርእሰ-መዲና ጅጅጋ 500 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በምትገኘውዶሀን ከተማ ነው፡፡ ለቤተሰቡ ሰባተኛ ልጅ ሲሆን፤ አምስት እህቶችእና ሦስት ወንድሞች አሉት፡፡ በጅጅጋ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት እስከ አስረኛ ክፍል ድረስ መዝለቁቢሳካለትም፤ ከዚህ በላይ ግን ሊቀጥል አልተቻለውም፡፡ ምክንያቱ ደግሞ የኢትዮጵያመንግስት የደህንነት ሠራተኞች የ1999ዓ.ም የግንቦት ሃያ በዓል በጅጅጋ ከተማ ስታዲዬም በተከበረበት ዕለት፣ የኦጋዴን ነፃአውጪ ግንባር (ኦብነግ) በሰነዘረው የቦንብ ጥቃት ተሳትፈሃል በሚል ለእስር በመዳረጉነው፡፡ ይህንን ተከትሎምከምድራችን አስከፊ ማሰቃያዎች መካከል ግንባር ቀደም በሆነውና የክልሉ
ነዋሪ “ጄል-አዳብ” (የገሃነም እስር ቤት) እያለ በሚጠራው ማጎሪያ ውስጥ እጅግ በጣም የከፋ ምድራዊ መከራ እንደተቀበለሀዘን በተጫነው ድምፅ ይናገራል፡፡ በሠውነቱ የተለያዩ ክፍሎች ላይ እንደ ፍም ቀልተው የሚታዩት ጠባሳዎቹም ያሳለፈውንሥቃይ አፍ አውጥተው ይመሰክራሉ፡፡ ለአራት ወራት ያህል አንድ ክፍል ውስጥ ለብቻው ተቆልፎበት፤ ሃያ አራት ሠዓታትሙሉ እጆቹ በካቴና ተቀፍድደው፣በቀን ከአምስት ጊዜ በላይ ለምርመራ እየተጠራ ያለዕረፍት ከባድ ስቅየት (ቶርቸር)ሲፈፀምበት ቆይቷል:፡ በመጨረሻም ለአንዲትም ቀን የፍርድ ቤት ደጅ ሳይረግጥ፣ ለኦብነግ አባላት አንድ ፓኬት ሲጋራሲያቀብል እጀ-ከፈንጅ ተይዟል በሚል ክስ የጅጅጋ ዞን ፍርድ ቤት በሞት እንዲቀጣ መወሰኑን እዛው እስር ቤት ሆኖከኢትዮጵያ ሬዲዮ የዜና እወጃ  እና ከቪኦኤ ሶማሊኛ ፕሮግራም ሠምቷል፡፡
ከፍርዱ በኋላም በተመ

Monday, December 1, 2014

ተማሪዎች፣ መምህራን እና የተቋማት ፕሬዚዳንቶች ለአመጽ ተነሱ!

ዘረኛውና አምባገነኑ የህወሓት አገዛዝ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ከካድሬ ማሰልጠኛ ማዕከላትነት ለይቶ የማያይ ስለመሆኑ በተቋማቱ ውስጥ የሚደረጉ ተግባራት ማረጋገጫዎች ናቸው። ለዚህ ተግባሩ በሰነድ ደረጃ መቅረብ ከሚችሉት የቅርብ ጊዜ ማስረጃዎች ዋነኛው በህዳር 2007 ዓ.ም. በሥራ ላይ የዋለው “የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የኢህአዴግ የምርጫ ድል ልማት ሰራዊት ግንባታ አደረጃጀት ማንዋል” የተሰኘው በትምህርት ሚኒስቴር ተዘጋጅቶ ለሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተላለፈው ሰነድ ነው። ይህ ሰነድ፣ የህወሓት አሳፋሪ የትምህርት ፓሊሲ ባፈጠጠ መልኩ የተገለፀበት፤ የኢፌዴሪ መንግሥት ተብሎ በሚጠራው የህወሓት አገዛዝ ተቋም እና በህወሓት/ኢህአዴግ ፓርቲ መካከል ለይምሰል እንኳን ልዩነት አለመኖሩ በግላጭ የሚታይበት ሰነድ በመሆኑ በዚህ ርዕሰ አንቀሳችን በስፋት ልንዳስሰው ወስነናል።

ሰነዱ በትምህርት ሥርዓቱ ላይ መርዙን መርጨት የሚጀምረው ገና በመግቢያው ስለማንዋሉ አስፈላጊነት ሲገልጽ ነው። ማንዋሉ “ከምንም በላይ የብጥብጥና የሁከት መንስኤ የሆነውን ተማሪ በኢህአዴግ አመራር አባላት እየታገዙ ለመያዝ የሚያስችል ነው” በማለት ህወሓት ተማሪውን የሚመለከተው “ከምንም በላይ በብጥብጥ መንስኤነት” መሆኑ፤ ለዚህ መድሀኒቱ ደግሞ ተማሪውን በኢህአዴግ አመራር አባላት “መያዝ” መሆኑን በማያሻማ ሁኔታ ይገልፃል። ቀጥሎም “በምርጫው ሊፈጠር የሚችለውን የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ሁከትና ብጥብጥ ለማስቆም በማደራጀት መረጃ ለመጥለፍ አመችነቱ የላቀ እንደሚሆን ታምኖበታል” በማለት መረጃ መጥለፍ የዩኒቨርስቲዎችና የትምህርት ሚኒስቴር ሥራ እንደሆነ አድርጎ ያቀርባል።