Monday, November 25, 2013

ኢትዮጵያዊው ቢንያም አሰፋ ከነቤተሰቡ ተገድሎ ተገኘ

(EMF) ከከተማው ራቅ ያለ ቦታ ነው የሚኖሩት – የ40 አመቱ ኢትዮጵያዊው ቢንያም አሰፋ፣ ጣልያናዊቷ ሚስቱ እና ልጆቹ። ድንገት በደረሰባቸው ጥቃት ባል እና ሚስቱ ከሶስት ወር ልጃቸው ጋር ሲገደሉ የአምስት አመት ልጃቸው ግን ተደብቃ ለማምለጥ ችላለች። ግድያው ከተፈጸመ በኋላ፤ የ5 አመቷ ልጅ ከተደበቀችበት ወጥታ ወደ ጎረቤት በመሄድ፤ “ቤተሰቦቼ ተጎድተዋል” ብላ ነገረቻቸው። ከዚያ በኋላ ነው ለፖሊስ የተደወለውና አሳዛኙ ድርጊት ይፋ የሆነው።
ቤን አሰፋ
በመጀመሪያ የሜሪላንድ ነዋሪ የሆኑት የቤን አሰፋ ቤተሰቦች የደረሰው አደጋ፤ የርስ በርስ ግጭት ሊሆን ይችላል፤ በሚል ብዙዎችን ሲያነጋግር ቆይቶ ነበር። ሆኖም ፖሊስ ዛሬ እንደገለጸው ከሆነ፤ ግድያው በሌላ ወገን የተፈጸመ ነው ተብሏል።

ፖሊስ የደረሰበትን የምርመራ ውጤት ይፋ አላደረገም። ይልቁንም የሟች (የቤን አሰፋ ሚስት) ቤተሰቦች ከጣልያን አገር ይገባሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው። እነሱ ወደ አሜሪካ ከገቡ በኋላ ፖሊስ የደረሰበትን የምርመራ ውጤት ይፋ እንደሚያደርግ ገልጿል።

ሁለቱም ባል እና ሚስቶች የባዮ ሜዲካል ህክምና ሳይንቲስቶች ነበሩ።

No comments:

Post a Comment