Wednesday, February 12, 2014

ተጠልፈው የተወሰዱት ሁለቱ የኦጋዴን ነጻ አውጭ ባለስልጣናት በአንድ ወታደራዊ ሆስፒታል ውስጥ ሲታከሙ መታየታቸውን ግንባሩ ገለጸ

የካቲት ፬ (አራት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ግንባሩ ለኢሳት በላከው መረጃ ፣ ከኢህአዴግ መንግስት ጋር ድርድር ለማድረግ በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ተገኝተው  በኢትዮጵያ የደህንነት ሃይሎች ታፍነው የተወሰዱት የኦብነግ አመራሮች፣ የደረሰባቸውን ከፍተኛ ድብደባ ተከትሎ በአንድ ወታደራዊ ሆስፒታል ውስጥ ሲታከሙ ታይተዋል። የመንግስት የደህንነት ሰራተኞች ” ባለስልጣኖቹ በገዛ ፈቃዳቸው እጃቸውን እንደሰጡ ለማሳመን ያደረጉት ከፍተኛ ጥረት ባለመሳካቱ  አሰቃቂ ድብደባ እንደተፈጸመባቸው” ግንባሩ አክሎ ገልጿል።
ገዢው ፓርቲ ከዚህ ቀደም አንዳንድ ሰዎችን በሃይል ወይም ገንዘብ በመስጠትና በማማለል ሰላም ስምምነት እንዲፈርሙ ሲያደርግ መቆየቱን ያስታወሰው መግለጫው፣ በሁለቱ ባለስልጣኖች ላይ የደረሰውም ከዚህ የተለየ አለመሆኑን አትቷል።
ግንባሩ የኬንያ መንግስት፣የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረትና የአውሮፓ ህብረት የኢህአዴግ መንግስት የሰዎቹን ደህንነት ጠብቆ እንዲለቃቸው ግፊት እንዲያደርጉ ጠይቋል።

No comments:

Post a Comment