Tuesday, February 24, 2015

በአዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች መፈክር የተፃፈባቸው ወረቀቶች ተበትነው አደሩ


በአዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች መፈክር የተፃፈባቸው ወረቀቶች ተበትነው አደሩ





አቡ ዳውድ ኡስማን
በአዲስ አበባ ትላንት ለሊቱን በተለያዩ አካባቢዎች ሙስሊሞችን የማሰር ዘመቻውን በመቃወም በራሪ ወረቀቶች ተበትነው እና ተለጥፈው ማደራቸውን ምንጮች አስታወቁ፡፡
ወረቀቶቹ በመንገድ ጋር ግድግዳዎች ላይ፣ በመንገድ ምልክቶች ላይ፣ በመብራት ፖሎች ላይ የተለጠፉ ሲሆን በየመንገዱም መበተናቸው ታውቋል፡፡
ትላንት ሌሊቱን ፒያሳ አምፒር አካባቢ፣ በሜክሲኮ ቄራ መንገድ ላይ፣ በጦር ሃይሎች፣በቦሌ ፒኮክ እና ወሎ ሰፈር፣ በመገናኛ፣ በመካኒሳ፣በቤተል እና በሌሎች ቦታዎች ላይ ወረቀት ተበትነው ማደራቸው ታውቋል፡፡
ከተበተኑት እና ከተለጠፉት መፈክሮች መካከል እስራት ትግላችንን አያስቆመውም፣መስዋትነት የኢስላም መንገድ ነው፣ሺ ሰው ቢታሰር ሺ ሰው ይተካል፣ ለኢስላም መታሰር ክብር ነው፣ ትግላችን ከምረጫው ቡሃላም ይቀጥላል፣ ድምፃችን ይሰማ፣ትግላችን ይቀጥላል የሚሉና ሌሎች በርካታ መልዕክቶችን የያዙ ወረቀቶች በመተናቸው ተገልፆል፡፡
መንግስት በአዲስ አበባ ሙስሊሞች የማሰር ዘመቻውን አጠናክሮ በቀጠለበት ወቅት ህዝበ ሙስሊሙ እስራት መፍትሄ እንደማይሆን በተግባር ያረጋገጠ መልዕክት በትላንትናው ለሊት አስተላልፏል::

No comments:

Post a Comment