Tuesday, September 1, 2015

አርበኞች ግንቦት 7 ሌላ የተሳካ የገንዘብ ማሰባሰብ ሂደት በኮሎራዶ ዴንቨር ማከናወኑ ተገለጸ

አርበኞች ግንቦት 7 ሌላ  የተሳካ የገንዘብ ማሰባሰብ ሂደት በኮሎራዶ ዴንቨር ማከናወኑ ተገለጸ
August 31st, 2015

በትላንትናው እለት በአሜሪካን ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ለአርበኞች ግንቦት 7 ድጋፍ የሚሆን የተሳካ የተባለለትን ቁጥሩ ወደ 400 የሚያህል ነዋሪዎች የተጀመረውን የነጻነት ትግል በመገኘት ተሳትፎአቸውን አሳይተዋል።



በእለቱ የአርበኖች ግንቦት 7 የምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ቸኮል ጌታሁን ለታዳሚው ትግሉን ለምን መደገፍ እንዳለብን እና በኤርትራ በኩል የሚደረግላቸውን ማናቸውም ድጋፍ በማመስገን ይህን የተሳሰረ ግንኙነት የወያኔ ፕሮፖጋንዳ ሊበጥሰው እንደማይገባ አስረግጠው ተናግረዋል። መወቀስ ካለብን እኛ ተቃዋሚዎች እንጂ አስተናጋጅ ሀገሮች አይደሉም። እኔ እዛ ደርሶ መምጣት እየሩሳሌም ደርሽ የመጣሁ ያህል ነው የሚሰማኝ። በእዚህ እድሜዪ ለሀገሬ ህልኢና የማይወቅሰኝን እያደረግኩ ነው። እናንተስ? እያንዳንዳችሁ በዚህ ቤት የምትገኙ ሁሉ ህሊናችሁ ንጹህ እንዲሆን ለሀገራችሁ አንድ ነገር አበርክቱ። ዛሬ የምታደርጉት በብርሃ ካለው ታጋዮቻችን ሂዎት ጋር ብንመነዝረው ከባድ ነው ስለዚህ መርዳት ብዙ የጠበቅባችሆል ብለዋል።

ሌላው ተናጋሪ ጋዜጠኛ አበበ ገላው የነበረ ሲሆን እንደወትሮው ሁሉ አቶ አበበ የትግሉን አስፈላጊነት እና እዚህ ደረጃ የደረሰበትን አድንቀው ዛሬ ሁሉም ኢትዮጵያኖች አንድ ሁነነን ሳንጠላለፍ ጥሩ አስተዋጽኦ እንዳርግ። ከአሉባልታ ወሬዎች ተቆጥበን ስራ ላይ መሰማራት አለብን። የሀሰት ፖረፐግናዳዎችን ማዳመጥ የለብንም። የኢትዮጵያ ህዝብ ከእኛ ብዙ ይጠብቃል እኛ የተጠበቅነውnንያህል ሆነን ለህዝባችን ለመገኘት እንደ አርበኞች ግንቦት 7 ያለ ጠንካራ ድርጅት መደገፍ የግድ ነው ሲል ለታዳሚው አብራርተዋል።

በገንዘብ ስብሰባ ሂደቱ ላይ አዘጋጁ ለጨራታ ቲዮታ ፒረስ ሃይብሪድ መኪና በማቅረብ ከፍተኘኛ ፍክክር በተደረገበት ይሄው ውድድር ጫራታው 47,200 ሺ የአሜሪካን ዶላር ተሽጦል። አሸናፊው በእለቱ የመኪናውን ቁልፍ ከጋዜጠኛ አበበ ገላው ተረክቦል።

የ4አመት ታዳጊ ኢትዮጵያዊ ህጻንም በጫራታው ላይ ሲሳተፍ ተስተውሎል በመጨረሻም ለታዳሚው እረ ጎራው… እማማ ኢትዮጵያ… እረ ጫካው….. የሚሊ ቀረርቶዎችንና ሽለላዎችን በማቅረብ ታዳሚውን ሲያዝናና አመሽቶል።

አዘጋጆቹ በእለቱ ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸው በጫራታ ብቻ $47,200 መሰብሰቡን ይህም ሌሎች የመግቢያና ሽያጮች እና መዋጮዎችን ያልጨመረ እንደሆነ ለዝግጅት ክፍላችን አስታውቀዋል። ምናልባትም ከዲሲ ግብረሃይል ዝግጅት ጋር ተመሳሳይ የሆነ ገቢ ይኖራቸዋል የሚል ግምት ተገምቶል።

ኮሎራዶ እንደዚህ አይነት ያለው መጠን ገንዘብ ሲሰበሰብ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ብለዋል። በተጨማሪም በኮሎራዶ የሚገኙ እና በዴንቨር ኢንተርናሽናል ኤርፖርት የሚሰሩ ኢትዮጵያኖች በመሰባሰብ ለአርበኞች ግንቦት 7 ያዋጡትን ደጎስ ያለ ገንዘብም ለድርጅቱ ተወካይ በአዳራሹ አስረክበዋል።

በመጨረሻም አያውቁንም በሚለው ሙዚቃ የእለቱ ፕሮግራም ተዘግቶል።

No comments:

Post a Comment