Thursday, November 21, 2013

ኢትዮጵያ፣ በህዳርና በ… ሁልጊዜ አስታውሳለሁ!! (ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገ/ማርያም)

November 21, 2013
ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገ/ማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ

የህዳር ወር በኢትዮጵያውያን በአሰቃቂነቱ ሁልጊዜ ሲታወስ ይኖራል፡፡

እ.ኤ.አ ኖቬምበር 2013 ሳውዲ አረቢያ ውስጥ በቃላት ለመግለጽ በሚዘገንን መልኩ በኢትዮጵያውያን/ት ላይ ሰቆቃ የተፈጸመበት ወር ነው፡፡ ላለፉት ጥቂት ዓመታት በሳውዲ አረቢያ በሚኖሩ፣ በሚሰሩና የፖለቲካ ጥገኝነት ለመጠየቅ ጥረት በማድረግ ላይ በሚገኙ ኢትዮጵያውያን/ት ላይ ስልታዊ የሆነ ጥቃት ሲሰነዘር ቆይቷል፡፡ እንዲያውም በግል በሚኖሩበት ቤት እምነታቸውን በማራመዳቸው ብቻ ኢትዮጵያውያኑ/ቱ ዜጎች ላይ የወንጀል ድርጊት ተፈጽሞባቸዋል፣ እንዲጋዙም ተደርጓል፡፡

እ.ኤ.አ 2011 የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቱ (Human Rights Watch) ዘገባ የሳውዲ አረቢያ ፖሊስ “ህገወጥ ስብሰባ በሚል ሰበብ 35 የክርስትና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያወያንን/ትን“ “በአንድ ኢትዮጵያዊ የክርስትና እምነት ተከታይ የግል መኖሪያ ቤት በእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል ዋዜማ ተሰባስበው ጸሎት በማድረግ ላይ እንዳሉ” በፖሊስ ቀጥጥር ስር ውለዋል” ይላል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በሳውዲ አረቢያ ጥገኝነት በሚፈልጉ እና ሌሎች ስደተኛ ኢትዮጵያውያት የቤት ሰራተኖች ላይ በሚደረገው ሰብአዊ መብት ረገጣ ምክንያት ምንጊዜም የማያቋርጥ ትችት እየተደረገ መሆኑን መግለጽ ማጋነን አይሆንም፡፡ በዚህ ወር በዕየለቱ በሚባል መልኩ የሳውዲ አረቢያ ፖሊሶች፣ የደህንነት ኃላፊዎችና ተራ የሳውዲ ዜጎች በየመንገዱ ኢትዮጵያውያን/ት ዜጎችን ያድናሉ፣ ይደበድባሉ፣ ያሰቃያሉ፣ አንዳንድ ጊዜም ይገድላሉ፡፡ የሳውዲ ፖሊሶች ኢትዮጵያውያንን ሲያሰቃዩ የሚያሳየው የቪዲዮ ቅርፅ ለህሊና የሚሰቀጥጥ ነው፡፡ የሳውዲዎች ኢትዮጵያውያንን በየመንገዱ የማባረር ሁከት፣ ጥቃት የመሰንዘርና የመግደል ድርጊት ምንም ዓይነት ማብራሪያ አያስፈልገውም፡፡ በአሁኑ ጊዜ ሳውዲ አረቢያ ውስጥ በኢትዮጵያውያን/ት ላይ የሚፈጸመውን የሰብአዊ መብት ረገጣ የሚያሳየው የፎቶግራፍ ምስል አስደንጋጭና ከሰለጠነ የሰው ልጅ አስተሳሰብ በእጅጉ የዘለለ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አስተዳደር 200 ሺ እና ከዚያ በላይ የሚሆኑትን በሳውዲ አረቢያ የሚኖሩትን ኢትዮጵያውያን/ት ለማገዝ ምን እያደረገ ነው? ምንም!!! እራሱ አምኖ በተቀበለው መሰረት ገዥው አስተዳደር ምን ያህል ኢትዮጵያውያን በሳውዲ አረቢያ እንደሚኖሩ እንኩዋን አያውቅም፣ ሆኖም ግን ተጨባጭነት በሌለው መልኩ ኢትዮጵያውያንን/ትን ከሳውዲ አረቢያ ሙሉ በሙሉ በተቻለ መጠን ወደ ኢትዮጵያ እመልሳለለሁ የሚል ቃል ገብቷል፡፡

የወባ ተመራማሪው “የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር”፣ ቴዎድሮስ አድሃኖም የሳውዲ መንግስት በግዛቱ በሚገኙት ስደተኛ ኢትዮጵያውያን/ት ሰራተኞች ላይ የፈጸመውን አረመኒያዊ የኃይል እርምጃ “መንግስቱ አውግዘዋል፡፡ ይኸ በፍጹም ተቀባይነት የለውም፡፡ ይህን ጉዳዩ የሳውዲ መንግስት እንዲያጣራ ጥሪ እናቀርባለን፡፡ እዚያ በነበሩበት ጊዜ በክብር መያዝ የነበረባቸውን ዜጎቻችንን ወደ ሀገራቸው ለመመለስም ደስተኞች ነን፡፡ ተቀባይነት የለውም” የሚለውን አባባል ገዥው አስተዳደር እንደ አስፈሪ የጭካኔ ድርጊቶች፣ ያለመሰልጠንነትና ዘግናኝ ጨካኝነትና ወንጀለኛነት የሚሉትን ቃላት ለመግለጽ የሚጠቀምበት የውግዘት ቃል ነው፡፡ አልጄዚራ እንደዘገበው ከሆነ በተፈጸመው ድርጊት ተበሳጭተው የነበሩ ኢትዮጵያውያን/ት አዲስ አበባ በሚገኘው የሳውዲ አረቢያ ኤምባሲ ፊት ለፊት በመገኘት ሰላማዊ ተቃውሟቸውን ለማሰማት በሄዱበት ጊዜ የገዥው አስተዳደር ፖሊስ በቁጥጥር በማዋል  ድብደባ ፍጽሞባቸዋል፡፡ “ፖሊሶች ከመጡ በኋላ ደብድበውናል፣ እና በአሁኑ ጊዜ ከ100 በላይ የሚሆኑ ሰዎች በእስር ቤት ይገኛሉ” በማለት የተቃዋሚው የሰማያዊ ፓርቲ ነባር አባል ጌትነት ባልቻ ገልጿል፡፡ ጌትነት በመቀጠልም “የፓርቲው ሊቀ መንበርና ምክትል ሊቀመንበር ከታሰሩት ውስጥ ይገኙበታል” በማለት ሀሳቡን አጠቃሏል፡፡

ሆኖም ግን ኢትዮጵያውያን/ት በሀዳር ወር መጎዳትና መጎሳቀል ለምን ይደንቀን? እ.ኤ.አ በኖቬምበር 2005 ያለው የገዢ አስተዳደር ለመናገር በሚዘገንን መልኩ የጭካኔ ድርጊት በአትዮጵያኖች ላይ ፈፅሞአል:: በዚያው ዓመት የፓርላማውን ምርጫ ተከትሎ በግንቦት ወር በጠራራ ፀሐይ የተዘረፈውን የህዝብ ድምጽ በመቀወም ድምጻቸውን ባሰሙ ኢትዮጵያውያን/ት ዜጎች እራሱ መለስ ዜናዊ ያቋቋመው አጣሪ ኮሚሽን 193 ያልታጠቁ ወንዶች፣ ሴቶች እና ልጆች በአዲስ አበባ መንገዶች በሰላማዊ መንገድ ተቃውሟቸውን በመግለጻቸውና እና ሌሎች በከፍተኛ ደህንነት በእስር ቤት የሚገኙ እስረኞችን ሆን ተብሎ በጥይት ደብድበዋል፣ ሌሎች 763 የሚሆኑት በጽኑ ቆስለዋል፡፡

እ.ኤ.አ ከ2007 ጀምሮ በየጊዜው በህዳር ወር እ.ኤ.አ የ2005 ምርጫን ተከትሎ በመቶዎች የሚቆጠሩ ጨዋና ያልታጠቁ ሰልፈኞች ተኩስ በመክፈት ገደሏቸው፣ አካለ ጎደሎ አደረጓቸው፡፡ እኔም ያንን ጊዜ ለማስታወሰ ስል መጻፌን ቀጥየ ነበር፡፡

በመጀመሪያው የማሰታወስ ጽሁፌ እ.ኤ.አ በኖቬምበር 2005 እና በጁን 2005 የተከፈለው መስዕዋትነት ለዘላለም ይታወሳል! ለአንባቢ ዎቼም ሳስታዉስ በህይወት ላሉትና ለሞቱት ምስክርነት መስጠት እንዳለባችሁ የሞራል ግዴታ ተጥሎባችኋል ብዬ ነበር፡፡ ኤሊ ዌይሰል የዕልቂቱ ተራፊና የኖቬል ተሸላሚ በክብር እንዳስቀመጠው “ማስታዋስ አለብን ምክንያቱም የጋራ ትውስታችን የሆኑትን ያለፉ ድርጊቶች የወደፊቱን ትውልድ መብት መከልከል ስለማንችል ነው መርሳት መጥፎ ነገር ብቻ አይደለም ነገር ግን ስድብም ነው፡፡ የሞቱትን መርሳት ሁለተኛ ከመግደል እኩል ነው፡፡”

በ2005 ያለቁትን መርሳት ማለት በእነርሱ ላይ የተፈጸሙትን ግፎች መርሳት እንዲህም ያሉትን አረመኔአዊ ወንጀል መርሳትማለት ነው፡፡ እልቂቱን መርሳት ማለት ወንጀለኞች ተጠያቂ እንዳይሆኑ የልብ ልብ መስጠት ማለት ነው፣ ምክንያቱም ወንጀሎቹ ተረስተዋል፡፡ በመጨረሻም መርሳት ማለት በስልጣን ላይ ያሉ ወንጀለኞች እንደገና እና እንደገና የወንጀል ደረጃውን ከፍ በማድረግና ተጠያቂነት የሌለበትን ሁኔታ በመፍጠር ወንጀል እንዲሰሩ ማበረታታት ማለት ነው፡፡

አስታውሳለሁ! በምንም አይነት አልረሳምም፣ በፍጹም!!!

አስታውሳለሁ ምክንያቱም እኔ ካላስታወስኩ ማን ያስታዉሳል? አስታውሳለሁ ምክንያቱም የምረሳ ከሆነ ወንጀሎችና ወንጀለኞች ይረሳሉ፡፡ የምረሳ ከሆነ ታሪክ እንዴት ሊያስታውስ ይችላል? ታሪክ ሊያስታውስ የሚችለው ሌላ ሊያስታውስ የሚችል ሰው ሲኖር ነው:: በህዳር፣ በታህሳስ፣ በጥር፣ በየካቲት፣ መጋቢት፣ ሚያዝያ… ዛሬ ለኢትዮጵያ ወጣቶችና ነገ ለሚወለዱ ህጻናት አስታውሳለሁ፡፡

የእኔን ስራ በማድነቅና ለበርካታ ዓመታት ሲደግፉ ሲቆዩ ሌሎች ደግሞ ሲተቹ ሲቃወሙ የሚኖሩ አሉ። እኔ በኢትዮጵያውያን ሰበአዊ መብቶች ችኮ ነው ይሉኛል:: በኢትዮጵያውያን ሰበአዊ መብቶች ችኮ መሆን ለኔ ታላቅ ክበር ነው::

የ2005 ዕልቂትን አስታውሳሁ፡፡ እያንዳንዱን በግፍ የተገደሉትን አስታዉሳለሁ፡፡ አስታውሳለሁ ወጣት ሴቶች ወደፊት እናት ላይሆኑ፣ ወጣት ወንዶችን የአራዊቱን  ጭፍረኞች ገዳዮችን አልረሳም  ወደፊት አባት ላይሆኑ፣ ወላጅ የሌላቸውን ወላጆቻቸው የተገደሉባቸውን አስታውሳለሁ፡፡ ልጆቻቸው የተገደሉባቸውን እናቶችንና አባቶችን አስታውሳለሁ::

ወንጀለኞችን አልረሳም፣ ተንኮል የሰሩትን 237ቱን የፖሊስ አባላት አስታውሳለሁ፣ የወንጀለኞችን ቁንጮና መሪ የነበረዉን አራዊትን  አልረሳም:: የአራዊቱን  ጭፍረኞች ገዳዮችን አልረሳም::

አስታውሳሁ፣ መቼ ረሳለሁ: ሁልጊዜ  ህዳርን፣ ታህሳስን፣ ጥርን፣ የካቲትን፣ መጋቢትን፣ ሚያዝያን…. አልረሳም፡፡

ተ.ቁ

ስም

ጾታ

እድሜ

ስራ



መግለጫ

1

ሬቡማ ኢርጋታ


34

ግንበኛ

2

መለሳቸው አለምነው


16

ተማሪ

3

ሀድራ ኦስማን


22

አይታወቅም

4

ጃፋር ኢብራሂመ


28

ቢዝነስ

5

መኮንን


17

አይታወቅም

6

ወልደሰማያት


17

7

ባህሩ ደምለው


አይታወቅም

8

ፈቀደ ነጋሽ


25

መካኒክ

9

አብርሀምይልማ


17

ታከሲ ነጂ

10

ያሬድ እሸቴ


23

ቢዝነስ

11

ከበደ ገ/ህይወት


17

ተማሪ

12

ማቴዎስ ፍልፍሉ


14

ተማሪ

13

ጌትንት ወዳጆ


48

ቢዝነስ

14

ቃሰም ራሽድ


21

መካኒክ

15

ሸውሞሊ


22

ቢዝነስ

16

አሊየ ኢሳ


20

የቀን ስራ

17

ሣምሶን ያዕቆብ


23

የህዝብ ማመላ

18

አለባለው አበበ


18

ተማሪ

19

በልዩ ዛ


18

ትራንስ. ረዳት

20

ዩሱፍ ጀማል


23

ተማሪ

21

አብርሃም አገኘሁ


23

ትራንስ.ረዳት

22

መሀመድ በቃ


45

አርሶ አደር

23

ረዴላ አወል


19

የታክሲ ረዳት

24

ሀብታሙ ኡርጋ


30

ቢዝነስ

25

ዳዊት ፀጋዬ


19

መካኒክ

26

ገዛኸኝ ገረመው


15

ተማሪ

27

ዮናስ አበራ


24

አይታወቅም

28

ግርማ ወልዴ


38

ሾፌር

29

ደስታ ብሩ


37

ቢዝነስ

30

ለገሰ ፈይሳ


60

ቢዝነስ

31

ተስፋዬ ቡሽራ


19

ጫማ ጠጋኝ

32

ቢንያም ደገፋ


18

ስራ አጥ

33

ሚሊዮን ሮቢ


32

ትራንስ.ረዳት

34

ደረጀ ደኔ


24

ተማሪ

35

ነብዩ ሃይሌ


16

ተማሪ

36

ምትኩ ምዋለንዳ


24

ዶመስቲክ ሰራተኛ

37

አንዋር ሱሩር


22

ቢዝነስ

38

ንጉሴ ዋብግነ


36

ዶመስቲክ ሰራተኛ

39

ዙልፋ ሀሰን


50

የቤት እመቤት

40

ዋስይሁን ከበደ


16

ተማሪ

41

ኤርሚያስ ከበደ


20

ተማሪ

42

00428


25

አይታወቅም

43

00429
26

አይታወቅም

44

00430
30

አይታወቅም

45

አዲሱ በላቸው


25

አይታወቅም

46

ደመቀ አበበ


አይታወቅም

47

00432
22

አይታወቅም

48

00450
20

አይታወቅም

49

13903
25

አይታወቅም

50

00435
30

አይታወቅም

51

13906
25

አይታወቅም

52

ተማም ሙክታር


25

53

በየነ በዛ


25

አይታወቅም

54

ወሰን አሰፋ


25

አይታወቅም

55

አበበ አንተነህ


30

አይታወቅም

56

ፈቃዱ ኃይሌ


25

አይታወቅም

57

ኤሊያስ ጎልቴ


አይታወቅም

58

ብርሃኑ ዋርካ


59

አሸብር መኩሪያ


አይታወቅም

60

ዳዊት ሰማ


አይታወቅም

61

መርሀጽድቅ ሲራክ


አይታወቅም

62

በለጠ ጋሻውጠና


አይታወቅም

63

ብኃይሉ ተስፋዬ


20

አይታወቅም

64

21760
18

አይታወቅም

65

21523
25

አይታወቅም

66

11657
24

አይታወቅም

67

21520
21

አይታወቅም

68

21781
60

አይታወቅም

69

ጌታቸው አዘዘ


45

አይታወቅም

70

21762
75

አይታወቅም

71

11662
45

አይታወቅም

72

21763
25

አይታወቅም

73

13087
30

አይታወቅም

74

21571
25

አይታወቅም

75

21761
21

አይታወቅም

76

21569
25

አይታወቅም

77

13088
30

አይታወቅም

78

እንዳልካቸው ገብርኤል


27

አይታወቅም

79

ኃይለማርያም አምባዬ


20

አይታወቅም

80

መብራቱ ዘውዱ


27

አይታወቅም

81

ስንታየሁ በየነ


14

አይታወቅም

82

ታምሩ ኃይለሚካኤል


አይታወቅም

83

አድማሱ አበበ


45

አይታወቅም

84

እቴነሽ ይማም


50

አይታወቅም

85

ወርቄ አበበ


19

አይታወቅም

86

ፈቃዱ ደግፌ


27

አይታወቅም

87

ሸምሱ ካሊድ


25

አይታወቅም

88

አብዱዋሂደ አህመዲን


30

አይታወቅም

89

ታከለ ደበሌ


20

አይታወቅም

90

ታደሰ ፌይሳ


38

አይታወቅም

91

ሶሎሞን ተስፋዬ


25

አይታወቅም

92

ቅጣው ወርቁ


25

አይታወቅም

93

ደስታ ነጋሽ


30

አይታወቅም

94

ይለፍ ነጋ


15

አይታወቅም

95

ዮሀንስ ኃይሌ


20

አይታወቅም

96

በኃይሉ ብርሀኑ


30

አይታወቅም

97

ሙሉ ሶሬሳ


50

አይታወቅም

98

የቤት እመቤት
አይታወቅም

99

ቴዎድሮስ


23

አይታወቅም

100

ጫማ ሰሪ


ጫማ ሰሪ

101

በኃይሉ ብርሃኔ


30

አይታወቅም

102

ሙሉ ሶሬሳ


50

የቤት እመቤት

103

ቴዎድሮስ ኃይሌ


23

ጫማ ሻጭ

104

ደጄኔ ይልማ


18

መጋዝን ጠባቂ

105

ኡጋሁን ወልደገብርኤል


18

ተማሪ

106

ደረጀ ማሞ


27

አናጺ

107

ረጋሳ ፈይሳ


55

ላውንድሪ ሰራተኛ

108

ቴዎድሮስ ገብረዎልድ


28

የግል ንግድ

109

መኮንን ገ/እግዚአብሄር


20

መካኒክ

110

ኤሊያስ ገ/ጊዮርጊስ


23

ተማሪ

110

አብርሀም መኮንን


21

የቀን ሰራተኛ

111

ጥሩወርቅ ገ/ጻድቅ


41

የቤት እመቤት

112

ሄኖክ መኮንን


28

አይታወቅም

113

ጌቱ ምሀትተ


24

አይታወቅም

114

ክብነሽ ታደሰ


52

አይታወቅም

115

መሳይ ስጦታው


29

የግል ንግድ

116

ሙሉአለም ወይሳ


15

አይታወቅም

117

አያልሰው ማሞ


23

አይታወቅም

118

ስንታየሁ መለሰ


24

የቀን ሰራተኛ

119

ጸዳለ ቢራ


50

የቤት እመቤት

120

አባይነህ ሰራሴድ


35

ልብስ ሰፊ

121

ፍቅረማርያም ተሊላ


18

ሾፌር

122

አለማየሁ ገርባ


26

አይታወቅም

124

ጆርጅ አበበ


36

የግል ትራንስፖርት

125

ሀብታሙ ዘገየ


16

ተማሪ

126

ምትኩ ገ/ስላሴ


24

ተማሪ

127

ትዕዛዙ መኩሪያ


24

የግል ንግድ

128

ፈቃዱ ዳልጌ


36

ልብስ ሰፊ

129

ሸዋጋ ወ/ጊዮርጊስ


38

የቀን ሰራተኛ

130

አለማየሁ ዘውዴ


32

የቴክስታይል ሰራተኛ

131

ዘላለም ገ/ጻድቅ


31

የታክሲ ሾፌር

132

መቆያ ታደሰ


19

ተማሪ

133

ሀይልየ ሁሴን


19

ተማሪ

134

ፍስሀ ገ/ጻድቅ


23

የፖሊስ ተቀጣሪ

135

ወጋየሁ አርጋው


26

ስራ ፈላጊ

136

መላኩ ከበደ


19

አይታወቅም

137

አባይነህ ኦራ


25

ልብስ ሰፊ

138

አበበች ሆለቱ


50

የቤት እመቤት

139

ደመቀ ጀንበሬ


30

አርሶ አደር

140

ክንዴ ወረሱ


22

ስራ ፈላጊ 141

141

እንዳለ ገ/መድህን


23

የግል ንግድ

142

አለማየሁ ወልዴ


24

መምህር

143

ብስራት ደምሴ


24

መኪና አስመጭ

144

መስፍን ጊዮርጊስ


23

የግል ንግድ

145

ወሎ ዳሪ


18

የግል ንግድ

146

በሀይሉ ገ/መድህን


20

የግል ንግድ

147

ሲራጂ ኑሩ ሰይድ


18

ተማሪ

148

እዮብ ገ/መድህን


25

ተማሪ

149

ዳንኤል ሙሉጌታ


25

የቀን ሰራተኛ

150

ቴዎድሮስ ደገፋ


25

የጫማ ፋብሪካ ሰራተኛ

151

ጋሻው ሙሉጌታ


24

ተማሪ

152

ከበደ ኦርቄ


22

ተማሪ

153

ለሊሳ ፋጤሳ


21

ተማሪ

154

ጃገማ ባሻ


20

ተማሪ

155

ደበላ ጉታ


15

ተማሪ

156

መላኩ ፈይሳ


16

ተማሪ

157

እልፍነሽ ተክሌ


45

አይታወቅም

158

ሀሰን ዱላ


64

አይታወቅም

159

ሁሴን ሀሰን ዱላ


25

አይታወቅም

160

ደጀኔ ደምሴ


15

አይታወቅም

161

ዘመድኩን አግደው


18

አይታወቅም

162

ጌታቸው ተረፈ


16

አይታወቅም

163

ደለለኝ አለሙ


20

አይታወቅም

164

ዩሱፍ ኡመር


20

አይታወቅም

165

መኩሪያ ተበጀ


22

አይታወቅም

166

ባድሜ ተሻማሁ


20

አይታወቅም

167

አምባው ጌታሁን


38

አይታወቅም

168

ተሾመ ኪዳኔ


65

የጤና ባለሙያ

169

ዮሴፍ ረጋሳ


አይታወቅም

170

አብዩ ንጉሴ


አይታወቅም

171

ታደለ በሀጋ


አይታወቅም

172

ኤፍሬም ሻፊ


አይታወቅም

173

አበበ ሀማ


አይታወቅም

174

ገብሬ ሞላ


አይታወቅም

175

ሰይዴ ኑረዲን


አይታወቅም

176

እንየው ጸጋዬ


32

እረዳት ትራንስፖርት

177

አብዱራህማን ፈረጅ


32

የእንጨት ስራ ባለሙያ

178

አምባው ብጡል


60

የቆዳ ፋብሪካ ሰራተኛ

179

አብዱልመናን ሁሴን


28

የግል ንግድ

180

ጅግሳ ሰጠኝ


18

ተማሪ

181

አሰፋ ነጋሳ


33

አናጺ

182

ከተማ ኡንኮ


23

ልብስ ሰፊ

183

ክብረት እልፍነህ


48

የጥበቃ ሰራተኛ

184

እዮብ ዘመድኩን


24

የግል ንግድ

185

ተስፋዬ መንገሻ


15

የግል ንግድ

186

ካፒቴን ደበሳ ቶሎሳ


58

የግል ንግድ

187

ትንሳኤ ዘገየ


14

ልብስ ሰፊ

188

ኪዳና ሹክሩ


25

የቀን ሰራተኛ

189

አንዷለም ሺበለው


16

ተማሪ

190

አዲሱ ተስፋሁን


19

የግል ንግድ

191

ካሳ በየነ


28

ልብስ ሽያጭ

192

ይታገሱ ሲሳይ


22

አይታወቅም



የጸጥታ ኃይሎች እርስ በእርስ ባደረጉት የተኩስ ልውውጥ በጥይት የተገደሉ ሰዎች፣



193

ነጋ ገብሬ


194

ጀበና ደሳለኝ


195

ሙሊታ ኢርኮ


196

የሃንስ ሶሎሞን


197 አሸናፊ ደሳለኝ


198

ፈይሳ ገ/መንፈስ


በመቶዎቹ የሚቆጠሩትን የግድያ ሰለባዎች፣ አካለ ጎደሎዎች፣ ቁስለኞች፣ በኃይል የተመቱትንና ሰውነታቸው በጥይት የተበሳሱትን ሁሉ አስታውሳለሁ፡፡

እ.ኤ.አኖቬምበር 2/2005 ከቃሊቲእስርቤትለማምለጥሲሞክሩበታጣቂዎችበተከፈተተኩስበጥይትተደብድበውያለቁሰዎችስምዝርዝር፣

ተ.ቁ

ስም

ጾታ

የተከሰሱበት ጥፋት፣

1

ጠይብ ሸምሱ መሀመድ


ለትጥቅ አመጽ በማነሳሳት
2

ሳሊ ከበደ


ምንም ዓይነት ክስ አልተጠቀሰም
3

ሰፊው እንድሪስ ታፈሰ


በአስገድዶ መድፈር
4

ዘገዬ ተንኮሉ በላይ


በዝርፊያ ወንጀል
5

ቢያድግልኝ ታመነ


የተወነጀሉበት ያልታወቀ
6

ገብሬ መስፍን ዳኘ


የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
7

በቀለ አብርሃም ታዬ


በህዝብ ላይ ሁከት በመፍጠር
8

ጉታ ሞላ


የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
9

ኩርፋ መልካ ተሊላ


በማስፈራራት ወንጀል
10

በጋሻው ተረፈ ጉደታ


የህዝብን ሰላም በማደፍረስ ወንጀል
12

አብደልወሃብ አህመዲን


በዘርፊያ ወንጀል
13

ተስፋዬ አብይ ሙሉጌታ


ለትጥቅ አመጽ በማነሳሳት
14

አዳነ ቢረዳ


በነፍስ ማጥፋት ወንጀል
15

ይርዳው ከርሴማ


የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
16

ባልቻ አለሙ ረጋሳ


በዝርፊያ ወንጀል
17

አቡሽ በለው ወዳጆ


የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
18

ዋለልኝ ታምሬ በላይ


በአስገድዶ መድፈር
19

ቸርነት ኃይሌ ቶላ


በዝርፊያ ወንጀል
20

ተማም ሸምሱ ጎሌ


የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
21

ገብየሁ በቀለ አለነ


የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
22

ዳንኤል ታዬ ለኩ


የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
23

መሀመድ ቱጂ ቀኔ


የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
24

አብዱ ነጂብ ኑር


የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
25

የማታው ሰርቤሎ


በአስገድዶ መድፈር
26

ፍቅሩ ናትናኤል ሰውነህ


በማስፈራራት ወንጀል
27

ሙኒር ከሊል አደም


በህዝብ ላይ ሁከት በመፍጠር
28

ኃይማኖት በድሉ ተሸመ


ጽንፈኝትን በማራመድ
29

ተስፋዬ ክብሮም ተኬ


በዥርፊያ ወንጀል
30

ወርቅነህ ተፈራ ሁንዴ


የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
31

ሲሳይ ምትኩ ሁነኛ


በማጭበርበር ወንጀል
32

ሙሉነህ አይናለም ማሞ


የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
33

ታደሰ ሩፌ የኔነህ


በማስፈራራት ወንጀል
34

አንተነህ በየቻ ቁበታ


ለትጥቅ አመጽ በማነሳሳት
35

ዘሪሁን መርሳ


በንብረት ላይ ጉዳት በማድረስ ወንወጀል
36

ወጋየሁ ዘሪሁን አስፋው


በዝርፊያ ወንጀል
37

በከልካይ ታምሩ


የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
38

የራስወርቅ አንተነህ


በማጭበርበር ወንጀል
39

ባዝዘው ብርሀኑ


ግብረሰዶም በመፈጸም ድርጊት
40

ሶሎሞን እዮብ ጉታ


በአስገድዶ መድፈር ወንጀል
41

አሳዩ ምትኩ አራጌ


በማስፈራራት ወንወጀል
42

ጋሜ ኃይሉ ዘገዬ


በህዝብ ላይ ሁከት በመፍጠር
43

ማሩ እናውጋው ድንበሬ


በአስገድዶ መድፈር ወንጀል
44

እጂጉ ምናለ


በግድያ ሙከራ ወንጀል
45

ኃይሉ ቦስኔ ሀቢብ


የተቀደሰን ቦታ በማራከስ
46

ጥላሁን መሰረት


የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
47

ንጉሴ በላይነህ


በዝርፊያ ወንጀል
48

አሸናፊ አበባው


የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
49

ፈለቀ ድንቄ


የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
50

ጀንበሬ ድንቅነህ ቢለው


በህዝብ ላይ ሁከት በመፍጠር
51

ቶሎሳ ወርቁ ደበበ


የዝርፊያ ወንጀል
52

መካሻ በላይነህ ታምሩ


የህዝብን ሰላም በማደፍረስ
53

ይፍሩ አደራው


የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
54

ፋንታሁን ዳኘ


የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
55

ጥበቤ ዋቀኔ ቱፋ


ለትጥቅ አመጽ በማነሳሳት
56

ሶሎሞን ገብረአምላክ


የህዝብን ሰላም በማደፍረስ
57

ባንጃው ቹቹ ካሳሁን


በዝርፊያ ወንጀል
58

ደመቀ አበጀ


በግድያ ሙከራ ወንጀል
59

እንዳለ እውነቴ መንግስቴ


የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
60

አለማየሁ ጋርባ


እ.ኤ.አ በ2004 ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች አመጽ ጋር በተያያዘ መልኩ በቁጥጥር የዋሉ
61

ሞርቆታ ኢዶሳ


የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
ለምዘገባ፣ በዚህ እልቂት ላይ ተዋንያን የነበሩ 237 የተረጋገጠ የፖሊስ እና የደህንነት አባላት ዝርዝርን የያዘ ሰነድ ተቀምጧል፡፡

የኔሰው ገብሬን አስታውሳለሁ!

Yenesew Gebre from Dawro-Waka Ethiopia
የኔሰው ገብሬ
እ.ኤ.አ በ11/11/11 የኔሰው ገብሬ የተባለ የ29 ዓመት መምህር እና የሰብአዊ መብት ተሟጋች በደቡብ ኢትዮጵያ በዳውሮ ዞን በተርጫ ከተማ ከህዝብ መሰብሰቢያ ዳራሽ ፊት ለፊት እሳት በመለኮስ እራሱን በእሳት አያይዟል፡፡ ለሶስት ቀናት ቆስሎ ከቆየ በኋላ ህይወቱ ሊያልፍ ችሏል፡፡ እራሱን በእሳት ከማያያዙ በፊት የኔሰው ከህዝብ መሰብሰቢያ አዳራሽ ውጭ ለተሰበሰበ ህዝብ እንዲህ የሚል ንግግር አሰምቶ ነበር፣ “በእኩልነት ላይ ባልተመሰረተ አስተዳደር እና ፍትህ በሌለበት እንዲሁም የሰብአዊ መብት በማይከበርበት አገር ውስጥ እራሴን ለመስዋዕትነት አቀርባለሁ፣ ይህንንም በማድረጌ ወጣቱ ትውልድ ነጻ ይወጣል፡፡” የአትዮጵያ ጀግናዉ የእኔሰው ገብሬን አስታውሳለሁ…

“ገዳዮችን አስታውሳለሁ፣ የግድያ ሰለባዎችንም አስታውሳለሁ፣ ለትግሌ የሚያግዙ አንድ ሺ እና ከዚያ በላይ ያሉ አሳማኝ ምክንያቶች እና ተስፋ ቢኖረኝም፡፡ ባስታወስኩ ቁጥር ተስፋየ ይሟጠጣል፣ ያንን ድርጊት ባስታውስኩ ቁጥር ደግሞ ተስፋቢስነቴን የማስወገድ ኃላፊነት እንዳለብኝ እገነዘበላሁ፣ ተስፋ ከተስፋቢስነት በላይ ነው፡፡“ ይላል ኤሊ ዊሴል!

**ለጥቃቱ ሰለባዎች ተጨማሪ መረጃ ይሆን ዘንድ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ተሟጋች የሆኑት ያሬድ ኃ/ማርያም እ.ኤ.አ ሜይ 15/2006 “በሰው ልጆች ላይ የተፈጸመ  ወንጀል በኢትዮጵያ፣ የጁንና ኖቬምበር 2005 የአዲስ አበባው ዕልቂት“ በሚል ርዕስ ለአውሮፓ ህብረት ፓርላሜንት ለልማትና ውጭ ጉዳዮች እና ለሰብአዊ መብቶች ንዑስ ኮሚቴ አስቸኳይ ጥምር ጉባኤ የቃረቡትን ምስክርነት ይመለከቷል፡፡

***የመርማሪ ኮሚሽኑ ሪፖርት ሙሉ በሙሉ የጥቃቱ ሰለባዎችን ነጻ ሲያወጣ አጠቃላይ ኃላፊነቱን ግን በፖሊስና ታጣቂ ኃይሎች ላይ ደፍድፎታል፡፡ መርማሪ ኮሚሽኑ አስተያየቱን በመቀጠል እንደሚከተለው አጠቃሎታል፣ “በተቃዋሚዎቹ የተጎዳ ንብረት የለም፣ በመንግስት በሞኖፖል በተያዘው መገናኛ ብዙሀን እንደተለፈፈው ጥቂት ተቃዋሚዎች የእጅ ቦንቦችንና ጠመንጃዎችን ታጥቀዋል እንደሚለው ሳይሆን በተቃራኒው የእጅ ቦንብ እና ጠብመንጃ የታጠቀ አንድም የተቀዋሚ አባል የለም፣ በመንግስት ታጣቂ ኃይሎች የተከፈተው ተኩስ ሰላማዊ ሰልፈኞችን ለመበተን ሳይሆን በተቃራኒው የሰልፈኞችን ጭንቅላትና ደረት ለመበርቀስ ዒላማ ያደረገ ነበር፡፡” የመርማሪ ኮሚሽኑ የ193 የእልቂቱ ሰለባዎችን ስም ዝርዝር የያዘ ሰነድ የሚያካትተው እ.ኤ.አ ከጁን 6 – 8 እና ከኖቬምበር 1- 4/2005 በዚህ ጊዜ ብቻ ያለውን ድርጊት እንዲያጣራ ለአጣሪ ኮሚሽኑ የተሰጠው ስልጣን ነበር፡፡ አጣሪ ኮሚሽኑ ግን በፓርላማው ከተሰጠው የጊዜ ገደብ ውጭ ከህግ ውጭ በመንግስት የፖሊስና የደህንነት ኃይሎች የተፈጸሙ ግድያዎችን ስም ዝዝዝር ያገኘ ቢሆንም እነዚህ ግድያዎች ኮሚሽኑ እንዲያጣራ ተለይቶ ከተሰጠው ጊዜ ውጭ በመሆናቸ ለህዝብ ይፋ ሳያደርገው ቀርቷል፡፡

No comments:

Post a Comment