Tuesday, February 18, 2014

የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ስልጣን ለቀቁ

የካቲት ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኦህዴድ ሊቀመንበርና የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አለማየሁ አቶምሳ የስልጣን መልቀቂያ ጥያቄ ማቅረባቸውን ተከትሎ፣ ምከር ቤቱ እንዳሰናበታቸው የመንግስት የመገናኛ ብዙሀን ዘግበዋል። አቶ አለማየሁ መታመማቸው ከተዘገበ የቆየ ቢሆንም እስካሁን ከስልጣን ሳይወርዱ ቆይተው አሁን ለምን ለማንሳት እንደተፈለገ ግልጽ አይደለም።
በአፋር በቅርቡ በሚካሄደው የምክር ቤት ስበሰባ ላይ ፕ/ት አሊ ሴሮ ከስልጣን ሊነሱ እንደሚችል ለኢሳት የደረሱ መረጃዎች አመልክተዋል። ምንም እንኳ ኢሳት ከመንግስት በኩል መረጃውን በማግኘት ለማረጋገጥ ባይችልም፣ ህወሀት በአሊ ሴሮ ምትክ ሌሎች ሰዎችን ለመሾም ማቀዱን የሚያሳዩ ፍንጮች ደርሰውታል።

No comments:

Post a Comment