Thursday, October 31, 2013

ግልጽ ደብዳቤ ለአቶ ኃይለማርያም ደሣለኝ፣ (ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት)


የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊት ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት፣ ሕዝብ ያልተቀበላቸው አንቀጾች እንዳሉት ብንገነዘብም፣ዓለም የተቀበላቸውን የሰብአዊና የዲሞክራሲያዊ መብቶች ያካተተ ሙሆኑን እንረዳለን። በሕገ-መንግሥቱ ከተካተቱት አንቀጾች፣አንቀጽ 74 ከንዑስ አንቀጽ(1) እስከ (13) የተዘረዘሩት የእርሰዎ የጠቅላይ ሚነስትሩ ሥልጣንና ተግባሮች እንደሆኑ ያረጋግጣል ። ከሁሉም በላይ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 13 የተገለጸው ሕገ-መንግሥቱን የማክበርና የማስከበር ኃላፊነት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የሰጠው ሥልጣን መሆኑን በማያሻማ ሁኔታ ተገልጿል። ይህም ማለት በአገሪቱ ውስጥ ለሚታይ የሕግ መከበርም ሆነ መጣስ ፣ሕግ ያከበሩትን የመሾምና የመሸለም፤ሕግ የጣሱትን ደግሞ ለፍርድ የማቅረብ ከፍተኛ ኃላፊነትና ተጠያቂነት ያለበዎ መሆኑን ሕገ-መንግሥቱ ያረጋግጣል። በአጠቃላይ፣በሕገ-መንግሥቱ የተጓደሉትንና የተዛቡትን ጉዳዮች በማጥናትና በማስጠናት እንዲሟሉና እንዲቃኑ የማድረግ፣በአግባቡ ያሉትን በሥራ እንዲውሉ የማድረግ ብቸኛው ኃላፊ እርሰዎ እንደሆኑ ሕገ-መንግሥቱ ያዛል። ቀጣዩን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ


1 comment:

  1. የመድኃኒት ንግድ ሥራዬን ለማስፋፋት በተጠቀምኩበት ብድር ለመርዳት ሚስተር ቤንጃን ከሚያስፈልጓቸው በላይ አልፈዋል ፡፡
    እነሱ ለመስራት ወዳጃዊ ፣ ባለሙያ እና ፍጹም ዕንቁዎች ነበሩ ፡፡ እኔ ለማነጋገር ብድር የሚፈልግን ማንኛውንም ሰው እመክራለሁ ፡፡ Lfdsloans@outlook.com.WhatsApp ... +19893943740.

    ReplyDelete